ኤቲዝምና አደጋው፦

ኤቲዝምና አደጋው፦
ኤቲዝም፣በታመመ እሳቤም ሆነ ጤናማ ባልሆነ ምልከታ፣ወይም በአፈንጋጭነት በግትርነትና በትዕቢት ብቻ የፈጣሪን ﷻ መኖር ማስተባበል ነው። ኤቲዝም ባለቤቱን ከተጨባጭ ቁሳዊ ነገሮች ውጭ ሌላ ነገር ማየትና መገንዘብ እንዳይችል የሚያደርግ አመለካከተ ውስንነት፣ልበ ጨለማነትና የአእምሮ የአስተሳሰብ እንከንና የሕሊና ጽልመት ነው። በዚህም በሰው ልጆችና በእምነቶቻቸው ላይ የማቴሪያሊዝምን የአስተሳሰብ ጎራ እሳቤዎችን በመጫን፣ለጥመትና ለዕድለ ቢስነት ይዳርጋል። ሰብአዊ ፍጡር፣በሌላው የተፈጥሮ ቁስ ላይ የሚተገበሩ ሕግጋት የሚተገበሩበት ተራ ቁስ ነው ብሎም ያምናል።

ይህ ሁሉ ወደ ሌጣ ቁሳዊነት፣ከመንፈስ ደስታና ከሕሊና እርጋታ ወደተራቆተው ወደ ሻካራው ራሽናሊዝም እንዲያዘነብል በመገፋፋት የሰውን ልጅ ለአደጋ ያጋልጠዋል። ኢአማኝ የሆነ ሰው በአምላክ መኖር የማያምን እስከሆነ ድረስ፣ቅጣትም ሆነ የአምላክን ቁጣ የማይፈራ ያሻውን ነገር ባሻው ሰዓት የሚፈጽም ይሆናል። ይህ ደግሞ በአላህ ﷻ መካድና የርሱን መብት ለሌላው መስጠት ከመሆኑም ባሻገር፣ሰብአዊ ተፈጥሮን ለብልሽትና ለውድመት አደጋ የሚያጋልጥ ነው። ለዚህ ነው ራስን የመግደል ወንጀል በኤቲስት ርእዮተኞች፣በምሁራንና በገጣሚያን ታሪክ ውስጥ በዝቶ የምናገኘው። ታሪክ በነዚህ ሁነቶች የተሞላ ነው፤ጥናቶችም ይህንኑ ያረጋግጣሉ። የዓለም ጤና ድርጅት WHO ኤክስፐርቶች የሆኑት ዶክተ ጆስ ማኑኤልና ተመራማሪ አልሳንደራ ፍሌሽማን ያካሄዱት ጥናት፣ በሃይማኖትና ራስን በማጥፋት መካከል ያለውን ግንኙነት በሚገልጸውና ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ ራሳቸውን በብዛት የሚገድሉት ኢአማኝ ኤቲስቶች መሆናቸውን ያረጋግጣል። ዝርዝሩ በተከታዩ ዲያግራም ቀርቧል፦

ራስን የመግደል አማካይ ቁጥር (ከያንዳንዱ 100000)

ድምር

ወንዶች

ሴቶች

ኤቲስቶች

ሙስሊሞች

ህንዱዎች

ክርስቲያኖች

ቡድሂስቶች

ከርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የሌለ በሆነው አላህ ማመን ከሥራዎች ሁሉ ዋነኛውን ቦታ፣ከሁሉም በላይ ክቡር የሆነውን ደረጃና የመጠቀ ስፍራን ይይዛል።

ኢማም አሽሻፊዒ



Tags: