ከእኽላስ ፍሬዎች መካከል፦

ከእኽላስ ፍሬዎች መካከል፦
1- የሥራዎች ተቀባይነት፦

ይህ እጅግ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ሲሆን፣እኽላስ ሥራዎች አላህﷻ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖራቸው መሟላት ያለበት ዋነኛው መስፈርት (ሸርጥ) ነው። ነቢዩﷺ ይህን በማስመልከት እንዲህ ብለዋል፦

‹‹አላህ ﷻ ከሥራ ለርሱ ብቻ ተብሎ በፍጹምነት (በእኽላስ) የተሰራውንና የርሱ ፊት የታለመበትን ብቻ እንጂ አይቀበልም።››

(በነሳኢ የተዘገበ)

በተጨማሪም ነቢዩﷺ እንዲህ ብለዋል፦

‹‹አላህ ﷻ ይህችን ኡምማ የሚያግዘው በደካሞቿ፣በዱዓቸው፣በሶላቶቻቸውና በፍጹምነታቸው (በእኽላሳቸው) ነው።››

(በነሳኢ የተዘገበ)

2-

የልቦና ሰላምና ከበሽታዎች ነጻ መሆን፦

ይህ እንደ ጥላቻ፣ክህደት፣እምነት ማጉደልና ምቀኝነት ካሉ የውስጥ ደዌዎች ነጻ መሆን ማለት ነው። የአላህ መልክተኛ ﷺ በመሰናበቻው ሐጅ ላይ እንዲህ ብለዋል፦

‹‹በሦስት ነገሮች እስከተካነ ድረስ የሙስሊም ልብ በክህደትና በመናፍቅነት በሽታ አይጠቃም እነሱም፦ ሥራን ለአላህ ብቻ ፍጹም ማድረግ፣ሙስሊም መሪዎችን መምከር፣የሙስሊሞችን ኅብረት (ጀማዓቸውን) አጥብቆ መያዝ ሲሆኑ፣ጥሪው ከጀርባቸው ያሉትንም ያጠቃልላል።››

(በትርምዚ የተዘገበ)

እብኑ ዑመር እንዲህ ብለዋል፦ አላህ ﷻ አንዲቷን ሱጁድና የአንዲት ድርሃም ምጽዋት ከኔ መቀበሉን ባውቅ ኖሮ፣ርቆ ከሚገኝ ነገር ሁሉ ከሞት ይበልጥ ለኔ የተወደደ ባልኖረ ነበር። አላህ ከማን እንደሚቀበል ታውቃለህን?

(إِنَّمَا يَتَقَبَّلُ ٱللَّهُ مِنَ ٱلۡمُتَّقِينَ ٢٧) [المائدة: 27] .

‹‹አላህ የሚቀበለው እኮ ከጥንቁቁቹ ብቻ ነው።›› [አልማኢዳህ፡27]

4- ዓለማዊ ሥራን ከመንፈሳዊ በጎ ሥራ ጋር ማጣመር ፦

ነቢዩﷺ እንዲህ ብለዋል፦

‹‹አንዳችሁ (ከሚስቱ ጋር) ግብረ ሥጋ መፈጸሙ ምጽዋት (ሶደቃ) ነው›› ሲሉ፣የአላህ መልክተኛ ሆይ! አንዳችን የራሱን ሥጋዊ ፍላጎት በማርካቱ ምንዳ ያገኝበታል ማለት ነው?! ብለው ጠየቋቸው። ‹‹ሐራም በሆነ ግንኙነት ያን ፈጽሞ ቢሆን ኖሮ ኃጢኣቱን ይሸከም የለምን?! እንደዚያው ሁሉ ሐላል በሆነ ግንኙነት በመርካቱ ምንዳ ያገኝበታል።›› አሉ።

(በሙስሊም የተዘገበ)

5- ሰይጣናዊ ሀሳቦችን፣ክፉና ጎትጓች ግምቶችን ማበረር፦

አላህﷻ ከእዝነቱ ጎራ ሲያባርረውና ከቸርነቱ ሲያርቀው ሰይጣንን አስመልክቶ እንዲህ ብሏል፦

(قَالَ رَبِّ بِمَآ أَغۡوَيۡتَنِي لَأُزَيِّنَنَّ لَهُمۡ فِي ٱلۡأَرۡضِ وَلَأُغۡوِيَنَّهُمۡ أَجۡمَعِينَ٣٩إِلَّا عِبَادَكَ مِنۡهُمُ ٱلۡمُخۡلَصِينَ ٤٠)

‹‹(ኢብሊስ) አለ፦ ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፤መላቸውን አጠማቸውም አለሁ፤ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ።››

[አልሒጅር፡39-40]

6- ችግሮችንና መከራዎችን ማስወገድ፦ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው በቡኻሪና ሙስሊም በተዘገው ሐዲሥ ውስጥ የሰፈረውና ዋሻ ውስጥ ለማደር ተገደው የዋሻው አፍ የተዘጋባቸው የሦስቱ ሰዎች ታሪክ ነው።

7- ከፈተናዎች አደጋ ነጻ መሆንና መዳን፦ በዚህ ረገድ የነቢዩ ዩሱፍ  ገጠመኝ ሁሌም ይጠቀሳል። ይህንኑ በማስመልከት አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

(وَلَقَدۡ هَمَّتۡ بِهِۦۖ وَهَمَّ بِهَا لَوۡلَآ أَن رَّءَا بُرۡهَٰنَ رَبِّهِۦۚ كَذَٰلِكَ لِنَصۡرِفَ عَنۡهُ ٱلسُّوٓءَ وَٱلۡفَحۡشَآءَۚ إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُخۡلَصِينَ٢٤)

‹‹በርሱም በእርግጥ አሰበች፤በርሷም አሰበ፤የጌታውን ማስረጃ ባላዬ ኖሮ፣(የተፈጥሮ ፍላጎቱን ባረካ ነበር)፤እንደዚሁ መጥፎ ነገርንና ኀጢአትን ከርሱ ላይ ልንመልስለት (አስረጃችንን አሳየነው)፤እርሱ ከተመረጡት ባሮቻችን ነውና።››

[ዩሱፍ፡24]

በአካሉ ከዱንያ የራቀ ብዙ ሰው በልቡ እውስጧ እየዳከረ ሊሆን ይችላል፤በአካሉ በውስጧ የሚገኝ ብዙ ሰው ደግሞ በልቡ ከርሷ ጋር የተቆራረጠ ሊሆን ሲችል ይኸኛው ከሁለቱ በጣም አስተዋዩ ነው።

8- የሥራ መጠን አነስተኛ ቢሆን እንኳ ምንዳን ማግኘት። አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

( وَلَا عَلَى ٱلَّذِينَ إِذَا مَآ أَتَوۡكَ لِتَحۡمِلَهُمۡ قُلۡتَ لَآ أَجِدُ مَآ أَحۡمِلُكُمۡ عَلَيۡهِ تَوَلَّواْ وَّأَعۡيُنُهُمۡ تَفِيضُ مِنَ ٱلدَّمۡعِ حَزَنًا أَلَّا يَجِدُواْ مَا يُنفِقُونَ ٩٢ )

‹‹በነዚያም ልትጭናቸው በመጡህ ጊዜ፣በርሱ ላይ የምጭናችሁ (አጋሰስ) አላገኝም ያልካቸው ስትኾን፣የሚያወጡት ገንዘብ ባለማግኘታቸው ለማዘናቸው ዓይኖቻቸው እንባን እያፈሰሱ በዞሩት ላይ (የወቀሳ መንገድ የለባቸውም)።››

[አልተውባህ፡92]

ነቢዩﷺ ይህን አስመልክተው እንዲህ ብለዋል፦

‹‹ሰማእትነትን (ሸሃዳን) ለማግኘት በፍጹም ልቦና አላህን የለመነን ሰው፣በመኝታው ላይ እያለ ቢሞት እንኳ አላህ ከሰማእታት ደረጃዎች ያደርሰዋል።››

(በሙስሊም የተዘገበ)

9- ጀነት መግባት። አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

( وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ ٣٩ )

‹‹ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም።››

[አልሷፍፋት፡39]

በተጨማሪም አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

(إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ٤٠ أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ٤١ فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ٤٢فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ٤٣عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ٤٤يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۢ٤٥بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ٤٦لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ٤٧وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ٤٨كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ٤٩)

‹‹ግን ምርጥ የኾኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)። እነዚያ ለነርሱ የታወቀ ሲሳይ አልላቸው። ፍራፍሬዎች፣(አሏቸው)፤እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤በድሎት ገነቶች ውስጥ። ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲኾኑ፣በአልጋዎች ላይ፣(ይንፈላሰሳሉ)። ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በነርሱ ላይ ይዝዞርባቸዋል። ነጭ፣ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፤በርሷ ውስጥም ምታት የሌለባትም፤እነርሱም ከርሷ የሚሰክሩ አይደሉም። እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፤እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ።››

[አልሷፍፋት፡40-49]

ይህ ከእኽላስ ፍሬዎች እጅግ የላቀው ነው።

ብዙውን ትንሽ ሥራ ንይያ ትልቀ ሲያደርገው፣ብዙውን ትልቅ ሥራ ንይያ ትንሽ ያደርገዋል።

እብን አልሙባረክ

መጥፎ ሥራዎችህን እንደምትደብቅ ሁሉ መልካም ሥራዎችህንም (ከታይታ) ደብቅ።

አቡ ሃዝም አልመዲኒይ



Tags: