የፍጹምነት (እኽላስ) ትርጉም፦

የፍጹምነት (እኽላስ) ትርጉም፦
ፍጹምነት የፍጹሞች (የሙኽሊሶች) ጀነትና አላህን የሚፈሩ ትጉሃን አገልጋዮቹ መንፈስ፣በፈጣሪና በባሪያው መካከል የሚገኝ ምስጢር ነው። መመጻደቅንና ልታይባይነትን ገቺ ነው። የሚሠራውን ሥራ አላህን ብቻ በማሰብና ለርሱ ብቻ ብሎ መሥራት ነው። ልብ ውስጥ ከአላህ በስተቀር ሌላ የሚታሰብ ነገር አለመኖር ነው። በሚሠራው ሥራ ከሰዎች ምንም ምስጋናም ሆነ ውዳሴ አለመጠበቅ ነው። የሥራን ዋጋ ከአላህﷻ ብቻ እንጂ ከማንም አለመጠበቅ ነው።

እኽላስ የሥራ ምልአትና ውበት ነው። በዱንያ ላይ በጣም ውዱ ነገር ነው። እኽላስ አላህንﷻ ብቻ የዕባዳ ዓላማና ግብ በማድረግ ዘውትር የርሱን ተቆጣጣሪነት እያሰቡ ፍጡራንን መርሳት ነው። ለርሱ ብቻ ተብሎ ለተሠራው ሥራ ቸሩ አላህ ﷻ ተገቢውን ምንዳ የሚሰጥ ሲሆን ለሌው ተብሎ የተሠራው ግን ከንቱ ልፋት ሆኖ ይቀራል። ነቢዩﷺ እንዲህ ብለዋል፦

‹‹ሥራዎች (የሚለኩት ከጀርባቸው ባለው ቁርጠኛ) ውሳኔ ነው፤እያንዳንዱ ሰውም በንይ'ያው መሰረት ነው የሚያገኘው፡፡ ስደቱ ወደሚያገኘው ዓለማዊ ጥቅም ወይም ወደሚያገባት ሴት የሆነ ሰው፣ስደቱ ለተሰደደበት ዓላማ ነው።››

(በቡኻሪ የተዘገበ)

አዩብ አስሰኽትያኒ ሌሊቱን ሙሉ በዕባዳ ያሳልፉ ነበር፤ሲነጋ ገና አሁን እንደ ነቁ ለማስመሰል ድምጻቸውን ከፍ ያደርጉ ነበር።

ፍጹምነት (እኽላስ) ያለው ደረጃ ፦

እኽላስ አቻ የሌለው የላቀ ደረጃ ያለው ሲሆን፣እኽላስ የሌለበት ሥራ ተቀባይነት የለውም። አላህﷻ ሥራችን እኽላስ እንዲኖረው ቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በብዙ አንቀጾች ያሳሰበ ሲሆን፣የሚከተሉት ጥቂቶቹ ናቸው፦

(وَمَآ أُمِرُوٓاْ إِلَّا لِيَعۡبُدُواْ ٱللَّهَ مُخۡلِصِينَ لَهُ ٱلدِّينَ)

‹‹አላህን ሃይማኖትን ለርሱ ብቻ አጥሪዎች፣ ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣. . እንጅ ያልታዘዙ ሲኾኑ (ተለያዩ)።››

[አልበይይናህ፡5]

አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

(قُلۡ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحۡيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ١٦٢لَا شَرِيكَ لَهُۥۖ وَبِذَٰلِكَ أُمِرۡتُ وَأَنَا۠ أَوَّلُ ٱلۡمُسۡلِمِينَ١٦٣)

‹‹ስግደቴ፣መገዛቴም፣ሕይወቴም፣ሞቴም፣ለዓለማት ጌታ ነው በል። ለርሱ ተጋሪ የለውም፤በዚህም (በማጥራት) ታዘዝኩ፤እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ (በል)።››

[አልአንዓም፡162-163]

በተጨማሪም አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

(ٱلَّذِي خَلَقَ ٱلۡمَوۡتَ وَٱلۡحَيَوٰةَ لِيَبۡلُوَكُمۡ أَيُّكُمۡ أَحۡسَنُ عَمَلٗا)

‹‹ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ፣ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው፤››

[አልሙልክ፡2]

በተጨማሪም እንዲህ ብሏል፦

(إِنَّآ أَنزَلۡنَآ إِلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ بِٱلۡحَقِّ فَٱعۡبُدِ ٱللَّهَ مُخۡلِصٗا لَّهُ ٱلدِّينَ٢أَلَا لِلَّهِ ٱلدِّينُ ٱلۡخَالِصُ)

‹‹እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በውነት (የተሞላ) ሲኾን አወረድነው፤አላህንም ሃይማኖትን ለርሱ ብቻ ያጠራህ ኾነህ ተገዛው። ንቁ! ፍጹም ጥሩ የኾነው ሃይማኖት የአላህ ብቻ ነው።››

[አልዙመር፡2-3]

አላህﷻ እንዲህ ብሏል፦

(فَمَن كَانَ يَرۡجُواْ لِقَآءَ رَبِّهِۦ فَلۡيَعۡمَلۡ عَمَلٗا صَٰلِحٗا وَلَا يُشۡرِكۡ بِعِبَادَةِ رَبِّهِۦٓ أَحَدَۢا١١٠)

‹‹የጌታውንም መገናኘት የሚፈልግ ሰው፣መልካም ሥራን ይሥራ፤በጌታውም መገዛት አንድንም አያጋራ፣በላቸው።››

[አልከህፍ፡11]



Tags: